በሰሜናዊ ህንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ30 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተሰማ

ሰብስክራይብ
በሰሜናዊ ህንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ30 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተሰማእሁድ እለት በህንድ ራጃስታን፣ ሂማቻል ፕራዴሽ፣ ኡታር ፕራዴሽ እና ፑንጃብ ክልሎች ውስጥ በትንሹ 31 ሰዎች እንደሞቱ ታይምስ ኦፍ ኢንድያ ጋዜጣ ዘግቧል።አብዛኛዎቹ ተጎጂዎች በራጃስታን ክልል ውስጥ እንደሆኑ የተነገረ ሲሆን በግዛቱ 17 ሰዎች ሲሞቱ ቢያንስ አምስት ሰዎች ጠፍተዋል።በአራት የሀገሪቱ ግዛቶች በትንሹ ስምንት ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱን ጋዜጣው ዘግቧል። በነሐሴ ወር መጀመሪያ የህንድ የዜና ወኪል ፕሬስ ትረስት እንደዘገበው በህንድ ሰሜናዊ ክፍል በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ20 በላይ ሰዎች ሞተዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0