የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ለውጥ ማነቃቂያ እንደሚሆን የህንድ ባለሃብት ተናገሩ የኢትዮጵያ ብረታብረት ኃ.የተ.የግ.ማ. ዋና ስራ አስፈጻሚ ባሄቬሽ ቻንዳሪያ የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የተቀዛቀዘውን ኢኮኖሚ በአዎንታዊው ይቀይራል ሲሉ ተስፋቸውን ገልጸዋል። ለዓመታት ስራ ላይ የቆየው ገዳቢ የቁጥጥር ፖሊሲ ለኢትዮጵያ የሚፈለገውን ውጤት አላስገኘም ብለዋል። ማሻሻያው ስር ነቀል እና ሁሉን አቀፍ እንደሆነ የተናገሩት ዋና ስራ አስፈጻሚው የውጭ ምንዛሪ መዛባት እና አለመመጣጠንን የመሳሰሉ የኢኮኖሚ ተግዳሮቶችን እንደሚቀርፍ አስረድተዋል። "ይህ ማሻሻያ ስር ነቀል ነው። ውጪ ያሉ ጓደኞቼ እና ባለሀብቶች ምን ዓይነት ውጤት ይዞ እንደሚመጣ ለማወቅ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ እየደወሉ ነው። አኔ ሁሉን አቀፍ፣ ሰፊ እና ቢዝነስን ግምት ውስጥ ያስገባ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ኮርፖሬቶች ከዚህ በላይ ሊጠይቁ አይችሉም” ሲሉ ለመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። ባለሀብቱ ማሻሻያው ለሸማቾች ከፍተኛ ወጪ፣ የአማራጭ ውስንነት እና ረጅም የጥበቃ ጊዜ ከፈጠረው ሻጭ ኢኮኖሚ ወደ ውጤታማ እና ፍትሃዊ የግብይት ኢኮኖሚ የሚያሸጋግር ወሳኝ እርምጃ ነው ብለዋል። "አንድ ሶስተኛ የሚሆነው የድሆች ወጪ ተሸፍኗል። መንግሥት ጭማሪውን የሚወስን እና የሚቆጣጠር ይሆናል። በማሻሻያው ነዳጅ፣ ማዳበሪያ፣ የምግብ ዘይት እና የምግብ እቃዎች በዓለም አቀፍ ኤጀንሲዎች እና መንግሥት በኩል ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ተካቷል" ብለዋል። "ኢትዮጵያ አሁን የሚያስፈልጋት ተስፈኝነት ነው። ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከአሳቢዎች፣ ከነጋዴዎች፣ ከሰራተኛ ማህበራት፣ ከባለሙያዎች እና እንደኛ ካሉ ባለሀብቶች ተስፈኝነት ያስፈልጋል" ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ለውጥ ማነቃቂያ እንደሚሆን የህንድ ባለሃብት ተናገሩ
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ለውጥ ማነቃቂያ እንደሚሆን የህንድ ባለሃብት ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ለውጥ ማነቃቂያ እንደሚሆን የህንድ ባለሃብት ተናገሩ የኢትዮጵያ ብረታብረት ኃ.የተ.የግ.ማ. ዋና ስራ አስፈጻሚ ባሄቬሽ ቻንዳሪያ የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የተቀዛቀዘውን ኢኮኖሚ በአዎንታዊው... 10.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-10T19:28+0300
2024-08-10T19:28+0300
2024-08-10T19:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ለውጥ ማነቃቂያ እንደሚሆን የህንድ ባለሃብት ተናገሩ
19:28 10.08.2024 (የተሻሻለ: 19:46 10.08.2024)
ሰብስክራይብ