የነሐሴ 3 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦

ሰብስክራይብ
የነሐሴ 3 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦🟠 ቭላድሚር ፑቲን ከሩሲያ የፀጥታ ምክር ቤት ቋሚ አባላት ጋር የስራ አፈጻጸም ውይይት አካሂደዋል። በስብሰባው ሽብርተኝነትን መዋጋት በተመለከቱ ጉዳዮች እንደተወያዩ የፌደራል የደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አሌክሳንደር ቦርትኒኮቭ ሪፖርት አድርገዋል። 🟠 የሩሲያ ሱ-34 ተዋጊ ጀት የዩክሬን ጦር አባላትን እና ቁሳቁሶችን ኩርስክ አቅራቢያ በሚገኘው ሱሚ ክልል በፋብ-3000 ቦምብ መምታቱን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 በሩሲያ ኩርስክ ክልል በዩክሬን በተፈፀመ ጥቃት 8 ህጻናትን ጨምሮ ሃምሳ አምስት ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው እንደሆነ የሩሲያ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሙራሽኮ ተናግረዋል። 🟠 የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሳምንቱ ማብቂያ ከመጀመሩ በፊት በድጋሚ የዋሽንግተን ስራቸውን ለቀው ወደ ሪዞርት ሄደዋል። የሀገሪቱ መሪ ዋይት ሃውስን ለቀው ወደ ዴላዌር ክፍለ ሀገር ሐሙስ ምሸት በረዋል። ፕሬዝዳንቱ ቀሪውን ሳምንት የሪዞርት ከተማ በሆነው ርሆበዝ ቢች ውስጥ በሚገኘው መኖሪያቸው ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0