ሩሲያ በአፍሪካዊቷ ሀገር በተካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ ወቅት የሩሲያ ባንዲራ መውለብለቡን አስመልክቶ " በናይጄሪያ በኩል የተወሰደው ጥንቃቄ የተሞላበት አካሄድ " ነው ብላለች

ሰብስክራይብ
ሩሲያ በአፍሪካዊቷ ሀገር በተካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ ወቅት የሩሲያ ባንዲራ መውለብለቡን አስመልክቶ " በናይጄሪያ በኩል የተወሰደው ጥንቃቄ የተሞላበት አካሄድ " ነው ብላለችበናይጄሪያ የሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ የፕሬስ ሴክሬታሪ ኃላፊ ዩሪ ፓራሞኖቭ ከስፑትኒክ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ወቅት እንዳሉት፤ የናይጄሪያ ባለስልጣናት “በተፈጠረው ነገር ላይ ሩሲያ እጇን አስገብታለች ከሚል ውንጀላ በመቆጠባቸው አመስግነዋል።ቀደም ሲል ናይጄሪያ በዚህ ሳምንት በተካሄደው ፀረ-መንግስት ሰልፎች ላይ የሩሲያ ባንዲራን አውለብልበዋል በሚል ሰባት የፖላንድ ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ይታወሳል።"በፖላንድ ዜጎች ላይ የተከሰተውን ክስተት በተመለከተ በመግለጫው ከተገለጸው በላይ ምንም ነገር ማከል አንችልም፤ ልክ እንደ ሀገሪቱ መንግስት በተቃውሞ ሰልፉ ወቅት የሩሲያ ግዛት ምልክት የሆነውን አርማ ይዘው በተገኙና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በቅርበት እየተከታተልን ነው። " ሲሉ ፓራሞኖቭ አክለው ገልፀዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0