የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት በግጭት ውስጥ የምትታመሰው ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን ለማረጋጋት ክልላዊ ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ በዛምቢያ አቻቸው ሃካይንዴ ሂቺሌማ ግብዣ በሀገሪቱ የሶስት ቀን ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳዪሺሚዬ በዛምቢያ ፓርላማ ባደረጉት ንግግር "በተለይ የኤም 23 አማፂያን በዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንደገና ማንሰራራቱ ያሳስበኛል" ብለዋል። ንዳዪሺሚዬ ቡሩንዲ ከታንዛኒያ እና ዲአርሲ ጋር የሚያዋስናትን ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ አንስተው ይህም የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ (ሳድክ) ወሳኝ አካል እንድትሆን እንደሚያደርጋት ተናግረዋል። "በቀጠናው የሰላም ጥረቶች እንደ ሽብርተኝነት፣ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እና የስደተኞች ቁጥር መጨመርን የመሳሰሉ ስጋቶችን ለመፍታ የበኩላችንን አስተዋፅኦ ለማበርከት ቡሩንዲ የሳድክ አባል የመሆን ፍላጎት አላት" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ቡሩንዲ እና ዛምቢያ በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ሰላም ለማስፈን የሚያደርጉትን ትብብር አድንቀዋል። ፕሬዝዳንት ንዳዪሺሚዬ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ድርቅ ከተመታችው ዛምቢያ ጋር አብሮነታቸውን ለማሳያት 5,000 ቶን ሩዝ፣ ባቄላ እና በቆሎ መለገሳቸውንም አስታውቀዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት በግጭት ውስጥ የምትታመሰው ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን ለማረጋጋት ክልላዊ ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ
የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት በግጭት ውስጥ የምትታመሰው ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን ለማረጋጋት ክልላዊ ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት በግጭት ውስጥ የምትታመሰው ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን ለማረጋጋት ክልላዊ ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ በዛምቢያ አቻቸው ሃካይንዴ ሂቺሌማ ግብዣ በሀገሪቱ የሶስት ቀን ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳዪሺሚዬ... 04.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-04T11:17+0300
2024-08-04T11:17+0300
2024-08-04T11:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት በግጭት ውስጥ የምትታመሰው ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክን ለማረጋጋት ክልላዊ ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ
11:17 04.08.2024 (የተሻሻለ: 11:46 04.08.2024)
ሰብስክራይብ