ቡርኪናፋሶ የተቀማጭ ገንዘብ ባንክ አቋቋመች

ሰብስክራይብ
ቡርኪናፋሶ የተቀማጭ ገንዘብ ባንክ አቋቋመች ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አርብ እለት በተካሂደው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ እንደተገኙ የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት በመዲናዋ ዋጋዱጉ ኩሉባ አካባቢ ይገኛል። የባንኩ ምስረታ ቡርኪናፋሶን "በልማት እጦት እና የገንዘብ እርዳታ ካሰሯት ጎታች ስልቶች እና አሰራሮች" ነፃ ያወጣታል ሲሉ የኢኮኖሚ ሚኒስትር አቡባካር ናካናቦ ተናግረዋል። ባንኩ አካውንት መክፈት፣ ሀብት መሰብሰብ እና ማስተዳደር እንዲሁም ግብይት መፈጸምን ጨምሮ የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። እንዲሁም ለደንበኞቹ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎቶችን ያቀርባል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0