🫘 የአፍሪካ ህብረት በአጀንዳ 2063 ቡናን እንደ ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ምርት አድርጎ መቀበሉ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሚኒስትር ተናገሩ

ሰብስክራይብ
🫘 የአፍሪካ ህብረት በአጀንዳ 2063 ቡናን እንደ ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ምርት አድርጎ መቀበሉ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሚኒስትር ተናገሩ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ በአዲስ አበባ በተካሄደው 37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ አህጉራዊው አካል ቡና በአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ውስጥ ያለውን ወሳኝ ሚና እና ለዘላቂ ልማት ያለውን አቅም ግንዛቤ ውስጥ በመክተት ቡናን የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ምርት አድርጎ ተቀብሏል። የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስትር እና የኢንተር አፍሪካ ቡና ድርጅት (አይ.ኤ.ሲ.ኦ) ዋና ሰብሳቢ ግርማ አመንቴ ይህ ውሳኔ ለአፍሪካ አህጉር የቡና ኢንዱስትሪ ትልቅ ቦታ ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ሲሉ አሞግሰዋል። ይህ እውቅና አይ.ኤ.ሲ.ኦ ልዩ የአፍሪካ ህብረት ኤጀንሲ ሆኖ ከመካተቱ ጋር ተዳምሮ የአፍሪካ የቡና ዘርፍ ላይ እሴት በመጨመር ለመለወጥ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል። "እንደ አህጉር በጋራ ስንሰራ ከዋጋ መጨመር ጋር ተያይዘው የሚመጡ ተግዳሮቶች እንደሚቀረፉ ያረጋገጠ ነው" ብለዋል ሚኒስትሩ። ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ የሰማያዊ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ ልማት ኮሚሽነር ጆሴፋ ሳኮ ይህንኑ ሀሳብ አስተጋብተው ውሳኔው ሌሎች የአፍሪካ ምርቶችን ለመለወጥ የሙከራ ተነሳሽነት መሆኑን አመልክተዋል። አፍሪካ 12% የቡና ፍሬ የምታመርት ሲሆን ከአህጉሪቱ አቅርቦት 62% የሚሸፍኑት ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ናቸው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0