የናይጄሪያ ፓርላማ ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያን ለመጨመር እና የፖሊስ ኢንስፔክተር ጄኔራልነት ጊዜን ለማራዘም የቀረቡትን ረቂቅ ህጎች አፀደቀ

ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ ፓርላማ ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያን ለመጨመር እና የፖሊስ ኢንስፔክተር ጄኔራልነት ጊዜን ለማራዘም የቀረቡትን ረቂቅ ህጎች አፀደቀሁለቱም ረቂቅ ህጎች በአንድ ቀን ውስጥ ለውይይት ቀርበው መፅደቃቸው፤ ህግ አውጭው ያለውን ጠንካራ ድጋፍ ያሳያል። የብሔራዊ የአነስተኛ ደሞዝ ህግ ማሻሻያ ዝቅተኛውን ደሞዝ ከ30,000 የናይጄሪያ ኒያራ ወደ 70,000 ያሳደገው በኑሮ ውድነቱን ሳቢያ ነው። ዝቅተኛው የደመወዝ ክፍያ ከኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር ያለውን ጠቀሜታ ለማረጋገጥ በየ 3 ዓመቱ አዲስ የግምገማ ዘዴን ይተገበራል። የፖሊስ ህጉ ማሻሻያ በናይጄሪያ ፖሊስ ሃይል ውስጥ የአመራር መረጋጋትን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፤ የፖሊስ ኢንስፔክተር ጄኔራልነትን ጊዜ በሹመት ደብዳቤያቸው ላይ በተገለጸው ጊዜ ልክ ያራዝመዋል።ሆኖም አንዳንድ ሴናተሮች በስልጣን መባለግ እና ዝቅተኛ የተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል በማለት ያላቸውን መቀነስ ላይ ስጋት ተናግረዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0