🪖 የሣህል ሕብረት ሀገራት በናይጄሪያ አዘጋጅነት በሚካሄደውና 51 ሀገራት በሚሳተፉበት የአፍሪካ ወታደራዊ ጨዋታዎች ላይ ይካፈላሉ

ሰብስክራይብ
🪖 የሣህል ሕብረት ሀገራት በናይጄሪያ አዘጋጅነት በሚካሄደውና 51 ሀገራት በሚሳተፉበት የአፍሪካ ወታደራዊ ጨዋታዎች ላይ ይካፈላሉ" ወታደራዊ ትብብርን በስፖርት ማበልፀግ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ወታደራዊ ጨዋታዎች፤ በአፍሪካ ሀገራት መካከል መልካም ግንኙነት እና ትብብር ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ በናይጄሪያ በመከላከያ ዋና መሥሪያ ቤት የስፖርት ዳይሬክተር ኤር ቫይስ ማርሻል አቢደሚ ማርኲስ አርብ ዕለት አስታውቀዋል።በቅርቡ በማሊ፣ በኒጀር እና በቡርኪናፋሶ የተካሄደውን ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ ከምዕራብ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ECOWAS) ማዕቀብ የተጣለባቸው ቢሆንም፤ ሀገራቱ ዝግጅቱን ይሳተፋሉ።ጨዋታው እ.አ.አ ከህዳር 5 እስከ 18 በናይጄሪያ ዋና ከተማ አቡጃ በሚገኘው በሞስሁድ አቢዮላ ብሄራዊ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን እግር ኳስ፣ ቦክስ እና ጁዶ ጨምሮ በሌሎች 19 የስፖርቶች ውድድሮች ይካሄዳሉ።በሱዳን ጦር ሃይሎች እና በፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች መካከል ግጭትእየተካሄደ ቢሆንም የሱዳን ጦር ዝግጅቱን ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0