ላይቤሪያ ፀረ ግብረ ሰዶም ህጓን እየከለሰች ነው።

ሰብስክራይብ
ላይቤሪያ ፀረ ግብረ ሰዶም ህጓን እየከለሰች ነው። የላይቤሪያ የተወካዮች ምክር ቤት የስርዓተ-ፆታ፣ የጤና እና የፍትህ አካላት ኮሚቴዎች የፀረ-ግብረ-ሰዶም ህግን ለማሻሻል የቀረበውን ሀሳብ እንዲያዩት ሃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። በተወካዩ ጆንሰን ኤስ ኤን ዊሊያምስ የቀረበው ረቂቅ ህግ ግብረ ሰዶምን ወንጀል ለማድረግ ያለመ ሲሆን እ.ኤ.አ የ1986 ህገ መንግስት ላይ የላይቤሪያን ባህል ለመጠበቅ የቀረበውን ድንጋጌ ለማክበር ነው። ረቂቅ አዋጁ በምክር ቤቱ ለውይይት ከቀረበ በኋላ ለበለጠ ግምገማ ወደ ኮሚቴው ተልኳል። ሕጉ ላይቤሪያ በግብረሰዶማውያን ጉዳይ ላይ ያላትን አቋም በግልፅ ያሳያል ሲሉ ዊሊያም ይገልፃሉ። በላይቤሪያ የተመሳሳይ ጾታ ድርጊቶች ቀድሞውኑም ቢሆን እስከ ሦስት ዓመት እስራት ያስቀጣል። "ሪፐብሊኩ የላይቤሪያውያንን አወንታዊ ባህል ይጠብቃል፤ ይከላከላል እንዲሁም ያስተዋውቃል፣ ከህዝባዊ እና ሀገራዊ እድገት ጋር የሚጣጣሙ ልማዳዊ እሴቶች ተቀብለው የላይቤሪያ ህብረተሰብ ፍላጎቶች ዋነኛ አካል ሆነው እንዲዳብሩ ያደርጋል" ሲል የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን የረቂቅ ሕጉን ሃሳብ ጠቅሶ ዘግቧል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0