በዲሞክራቲክ ኮንጎ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን መንግስት አስታወቀ

ሰብስክራይብ
በዲሞክራቲክ ኮንጎ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን መንግስት አስታወቀ የመንግስት ቃል አቀባይ ፓትሪክ ሙያያ በበሽታው የሞቱትን 450 ሰዎችን ጨምሮ የተጠረጠሩት ሰዎች ቁጥር 11,166 መድረሱን፤ እንዲሁም የገዳይነት ምጣኔውም በ4 በመቶ መጨመሩ  የሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሪፖርት አመላክቷል ብለዋል። ሪፖርቱ አክለውም “በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን” ኤ ኤፍ ፒ ዘግቧል። መንግስት በሽታውን ለመከላከል ተከታታይ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን በተለይም " የህክምና እንክብካቤ ማድረግ፤ ከሚመለከታቸው የዞን ጤና ኃላፊዎች ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር እና የማህበረሰብ አቀፍ ክትትልን ማሳደግ ላይ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። " ሪፖርቱ የወጣው ከቀናት በፊት የአለም ጤና ድርጅት (WHO) የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ ለአለም ስጋት ሊሆን ይችላል በሚል ማስጠንቀቁን ተከትሎ ነው። በዲሞክራቲክ ኮንጎ አዲስ እና ገዳይ የሆነ ቫይረስ ሊከስት ይችላል ሲል ድርጅቱ አስታውቋል። የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረእየሱስ እንዳሉት በቅርቡ የተከሰተው ወረርሽኝ “ የመቀነስ አዝማሚያ የለውም ” ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0