ሩሲያ አፍሪካ ውስጥ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ረገድ እየተጫወተች ያለውን የጨመረ ሚና ቶጎ ትገነዘባለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ሩሲያ አፍሪካ ውስጥ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ረገድ እየተጫወተች ያለውን የጨመረ ሚና ቶጎ ትገነዘባለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናገሩ "እኛ ሩሲያ በአህጉሪቱ ሰላም ለማስከበር እና ሽብርተኝነትን ለመከላከል እያደረገችው ላለው ድጋፍ ምስክሮች ነን" ሲሉ የቶጎ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሮበርት ዱሴይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል። የወታደራዊ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ የሥልጠና ድጋፍ እና የመረጃ ልውውጥ በርካታ የአህጉሪቱን ሀገራት እንደረዳም አክለዋል። "ምንም እንኳን ሽብርተኝነትን የመዋጋት ቀዳሚ ሃላፊነት የአፍሪካ ሀገራት ቢሆንም ሩሲያ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ ስር የምታደርገውን አስተዋጽኦ እናደንቃለን። ይሁን እንጂ ማንኛውም የውጭ እርዳታ ከአፍሪካዊ ተነሳሽነቶች ጋር የተጣጣመ እና የአፍሪካን ሉዓላዊነት ያከበረ ሊሆን ይገባል" ብለዋል ዱሴይ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0