ሩዋንዳውያን ፕሬዝዳንታቸውን ለመምረጥ በዛሬው ዕለት ድምፅ እየሰጡ ይገኛሉ። በህገ መንግስቱ መሰረት የምርጫው ዋና ዋና ህጎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ።

ሰብስክራይብ
ሩዋንዳውያን ፕሬዝዳንታቸውን ለመምረጥ በዛሬው ዕለት ድምፅ እየሰጡ ይገኛሉ። በህገ መንግስቱ መሰረት የምርጫው ዋና ዋና ህጎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ። ፕሬዝዳንቱ የሚመረጠው በሁለንተናዊ እና በሚስጥር በሚሰጥ ድምፅ ሲሆን የምርጫው ዘመን 5 አመት ነው። ምርጫው በአንድ ዙር ይካሄዳል። አንጻራዊ አብላጫ ድምፅ ያገኘ እጩ ተወዳዳሪ ፕሬዚዳንት ይሆናል። ሁለት እጩዎች ተመሳሳይ ድምጽ ካገኙ ግን ሁለተኛ ዙር ምርጫ ይካሄዳል። ፕሬዝዳንት ለመሆን ሩዋንዳ የተወለደ እና የሩዋንዳ ዜግነት ያለው መሆን አለበት። እጩ ተወዳዳሪው ዕድሜው 35 የሞላው እና የሌላ ሀገር ዜግነት የሌለው መሆን ይኖርበታል። የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት እና የተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የአንድ የፖለቲካ ድርጅት አባል ሊሆኑ አይችሉም። እ.ኤ.አ በ2015 በተካሄደው ህዝበ ውሳኔ ህገ መንግስቱ በመሻሻሉ ፖል ካጋሜ ለሶስተኛ ጊዜ ለሰባት አመት የስልጣን ዘመን እንዲወዳደሩ ፈቅዶላቸዋል። ይህ ከሁለት ተጨማሪ የአምስት አመታት የምርጫ ዘመን በኋላ መሆኑ ነው። ምርጫውን ለማከናወን ሥልጣን ያለው ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ነው። ማንኛውም ብቁ የሆነ እና 18 ዓመት የሞላው የሩዋንዳ ዜጋ  አመት የመምረጥ መብት አለው። የምርጫ ጣቢያዎች ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3፡00 ሰዓት ክፍት ይሆናልነው። የቅድመ ምርጫ ውጤት በ5 ቀናት ውስጥ ይፋ ይሆናል። የመጨረሻ ውጤት ደግሞ የቅድመ ምርጫ ውጤቱ ከተገለፀ በ7 ቀናት ውስጥ ይገለፃል። ተመራጩ ፕሬዝዳንት በጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። ተመራጩ ፕሬዝዳንት በ30 ቀናት ውስጥ ስራቸውን ይጀምራሉ። ፕሬዝዳንቱ የሀገር መሪ እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ናቸው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0