ደቡብ አፍሪካ የኒውክሌር ኃይል አጠቃቀሟን ለማሳደግ ትልቅ ጥረት ታደርጋለች ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ የኒውክሌር ኃይል አጠቃቀሟን ለማሳደግ ትልቅ ጥረት ታደርጋለች ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ የደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኬጎሲየንትሾ ራሞክጎፓ ሀገሪቱ ያለባትን የኤሌክትሪክ ሃይል እጥረት ለመቅረፍ የኒውክሌር ኢነርጂ ኢንዱስትሪዋን እንደምታሳድግ ጠቁመዋል። "ግልጽ ያልሆነ የግዥ አሰራር ሂደቱን ማጣጣል አንፈልግም፤ እርግጥ ነው ሀገራችን በምትችለው መጠን እና ፍጥነት ልክ የኃይል አቅርቦቱን እናደርገዋለን። ''ሲሉ ራሞክጎፓ ከመጀመሪያው የብሄራዊ አንድነት መንግስት ስብሰባ በፊት ለሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ተናግረዋል። አላማው በሚቀጥለው ወር የ2,500 ሜጋ ዋት ሃይል ማመንጫ የሚያስችል የግምጃ ቤት ፍቃድ ለማግኘት ሲሆን ከዚህ ቀደም የነበረው የግዥ ጥያቄ 9,000 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የሚያስቻል ነበር ተብሏል። "የግዥ አሰራሩ የፋይናንስ ድጋፍ ለማግኘት ከብሔራዊ ግምጃ ቤት ማፀደቅን ይፈልጋል፤ ስምምነቱን መጠን መገመት ትችላላችሁ"ብለዋል ሚኒስትሩ። " ከነሀሴ መጨረሻ በፊት ወጥተን ይህን ማድረግ እንደፈለግን እንናገራለን" ሲሉ ራሞክጎፓ ባለፈው እሁድ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0