ምዕራባውያን ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ አይደሉም ሲሉ በቴህራን የሩስያ አምባሳደር ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ምዕራባውያን ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ አይደሉም ሲሉ በቴህራን የሩስያ አምባሳደር ተናገሩ "አውሮፓውያን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓለም ዓቀፉ የአውቶሚው ኢነርጂ የገዢዎች ቦርድ ስብሰባ ላይ ፀረ-ኢራን መግለጫ ማውጣቱን መቀጠሉ ፤ምዕራባውያን ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ አለመሆናቸውን ያመለክታል፤ ገንቢ ውይይት እንዳይኖር እና ከኢራን ጋር በጎ ግንኙነት እንዳይኖር እያደረጉ ያሉት ምዕራባዊያን ናቸው ሲሉ በኢራን የሩሲያ አምባሳደር አሌክሲ ዴዶቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል። በተጨማሪም የጋራ የፀጥታ ስምምነት ድርጅት (CSTO) በካውካሰስ እና በኢራን ያለውን ሁኔታ እንዳይረጋጋ በምዕራቡ ዓለም የሚያደርጉትን ግልጽ ሙከራዎች እየተመለከ ይገኛል ሲሉ የጋራ የፀጥታ ስምምነት ድርጅት (CSTO )የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ቪክቶር ቫሲሊየቭ ተናግረዋል ። በተጨማሪም የምዕራባውያን አገሮች በአርሜኒያ አጎራባች አገሮች ውስጥ ጣልቃ ለመግባት እየሞከሩ ነው።ይህም የጋራ የፀጥታ ስምምነት ድርጅትን ጭምር ያሳስባል፤ምክንያቱም በእነዚህ አገሮች ውስጥ ያለው ሁኔታ ካልተረጋጋ፤የሁሉም የጋራ የፀጥታ ስምምነት ድርጅት አባል ሀገራት የጸጥታ ስጋቶች ይሆናል ብለዋል ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0