ጆርጅ ክሉኒ ባይደን እራሳቸውን እንዲያገሉ ጠይቆ ፕሬዝዳንቱ ከጊዜ ጋር ታግለው ማሸነፍ አይችሉም አለ

ሰብስክራይብ
ጆርጅ ክሉኒ ባይደን እራሳቸውን እንዲያገሉ ጠይቆ ፕሬዝዳንቱ ከጊዜ ጋር ታግለው ማሸነፍ አይችሉም አለ አሜሪካዊው ተዋናይ ጆርጅ ክሎኒ ኒውዮርክ ታይምስ ላይ በፃፈው አስተያየት "ጆ ባይደንን እንደ ሴናተር፣ እንደ ምክትልፕሬዝዳንት እና እንደ ፕሬዝዳንት እወዳቸዋለሁ። እንደ ጓደኛ አድርጌ እቆጥራቸዋለሁ፤ በእርሳቸውም አምናለሁ"ብሏል። "ባለፉት አራት አመታት ያጋጠሟቸውን ብዙ ፈተናዎች አልፈዋል። ነገር ግን ማሸነፍ የማይችሉት ትግል ጊዜን መዋጋት ነው።" ከሶስት ሳምንታት በፊት ተካሂዶ በነበረው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ላይ የነበሩት ባይደን ካሁኑ ጋር አይመሳሳሉም ሲል ያከለው ክሉኒ በ2010 ወይም 2020 የነበሩት ባይደን አሁን የሉም ብሏል፡፡ ቸክ ሹመርን እና ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ ከፍተኛ ዲሞክራቶች ከሴናተሮች እና ተወካዮች ጋር በመሆን ባይደን በፈቃዳቸው እንዲለቁ መጠየቅ አለባቸው ሲል የአስተያየት ፅሁፉ ጨምሮ ገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0