የግብፅ የዋጋ ግሽበት መቀነሱን ቢቀጥልም አሁንም ፈተናዎች ይቀራሉ

ሰብስክራይብ
የግብፅ የዋጋ ግሽበት መቀነሱን ቢቀጥልም አሁንም ፈተናዎች ይቀራሉ የሀገሪቱ የስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያሳየው በሰኔ ወር የዋጋ ግሽበት ለአራተኛ ተከታታይ ወር የቀነሰ ሲሆን በግንቦት ወር ከነበረበት 28.1% ወደ 27.5% ዝቅ ብሏል። እየታየ ያለው ቅናሽ የዋጋ ግሽበት 38% ደርሶ ከነበረበት መስከረም 2023 በኋላ የጀመረውን አዝማሚያ አስቀጥሏል። ካይሮ የዋጋ ግሽበትን ኢላማ ያደረገ ሞዴል እና ተለዋዋጭ የምንዛሪ ተመን መጠቀሟ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለታያው ለውጥ አስተዋጽኦ አንዳደረገ ይታመናል። ነገር ግን ተንታኞች ይህን አወንታዊ አዝማሚያ ሊያውኩ ስለሚችሉ ስጋቶች በተለይም እንደ ነዳጅ፣ መድሐኒት እና ማዳበሪያ ያሉ አስፈላጊ ሸቀጦች ላይ የሚኖር የዋጋ ጭማሪን አስጠንቅቀዋል። በቅርቡ የድጎማ የዳቦ ዋጋ ላይ የተደረገው የ300% ጭማሪ የምግብና መጠጥ ዋጋ ከዓመት ዓመት 30.8% እና ከወር ወር 3% እንዲንር አድርጓል። ዳቦ በአንፃራዊነት በሸማቹ ቅርጫት ውስጥ ያለው አነስተኛ ክብደት የጭማሬውን ተፅእኖ ቢገድበውም የሌሎች ምግቦች ዋጋ መቀነስ እና ጤናማ የዋጋ ለውጥ ጭማሬውን አካክሶታል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0