የሐምሌ 03 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦
🟠 ኔቶ አደጋዎችን ለመከላከል እና ውጥረት ለመቀነስ ከሞስኮ ጋር የግንኙነት መስመሮችን መቀጠል ይፈልጋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። ይህንን የሚመለከት አንቀጽ በህብረቱ ጉባኤ ረቂቅ መግለጫ ውስጥ ተካትቷል።
🟠 አሜሪካ እና አጋሮቿ ወደ ዩክሬን የላኳቸው ኤፍ-16 ተዋጊ ጀቶች በዚህ ክረምት ኪዬቭ እንደሚደርሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን ተናግረዋል።
🟠 አሜሪካ በ2026 የረዥም ርቀት መሳሪያዎችን በጀርመን ማሰማራት እንደምትጀምር ፔንታጎን አስታወቀ።
🟠 የዩክሬን የኔቶ አባልነት በህብረቱ እና በሩሲያ መካከል ቀጥተኛ ግጭት ስለሚፈጠር ጥያቄ ውስጥ የሚገባ አይደለም ሲሉ የሃንጋሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲጃርቶ ተናግረዋል።
🟠 የብሪክስ እንቅስቃሴ ዩናይትድ ስቴትስን ያናድዳል፤ በሀገራት ላይ ጫና ለመፍጠር ይሞክራሉ ነገር ግን የባለ ብዙ ዋልታ ዓለም ግንባታ ሂደት ሊቆም አይችልም ሲሉ የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሊቀመንበር ቫለንቲና ማትቪየንኮ ተናገሩ።
🟠 እስራኤል ደማስቆ በ1974 በጎላን ተራሮች የተቋቋመውን የግጭት መከላከያ ክልል ጥሳለች በማለት የሶሪያ ጦር ሰራዊት መሰረተ ልማት ላይ ጥቃት አድርሳለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የሐምሌ 03 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦
የሐምሌ 03 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦
Sputnik አፍሪካ
የሐምሌ 03 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 ኔቶ አደጋዎችን ለመከላከል እና ውጥረት ለመቀነስ ከሞስኮ ጋር የግንኙነት መስመሮችን መቀጠል ይፈልጋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። ይህንን የሚመለከት አንቀጽ በህብረቱ ጉባኤ ረቂቅ መግለጫ ውስጥ ተካትቷል። 🟠... 10.07.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-07-10T21:28+0300
2024-07-10T21:28+0300
2024-07-10T21:40+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий