ሪፐብሊክ ኮንጎ የአፍሪካ የደን መልሶ ልማት ጉባኤን እያስተናገደች ነው።

ሰብስክራይብ
ሪፐብሊክ ኮንጎ የአፍሪካ የደን መልሶ ልማት ጉባኤን እያስተናገደች ነው። ኮንፈረንሱ በ2023 በግብፅ COP27 ጉባኤ ላይ በኮንጎው ፕሬዝዳንት ዴኒስ ሳሱ ንጉሶ የጀመሩት "አፍሪካዊ እና አለም አቀፍ የደን ልማት እና የደን መልሶ ማልማት የአሥር ዓመት እቅድ " አካል መሆኑን ኤ ኤፍ ፒ ዘግቧል። "ይህ ኮንፈረንስ የጥናት ሂደት እና ህይወት የማዳን ምላሽ መጀመሪያ ይመስላል። እንደሚታወቀው የአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል" ሲሉ ሳሶ ንጌሶ ተናግሯል። "እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ ግልጽ ነው፤ሁሉም ነገር ለመስራት ፍላጎት እና አስፈላጊውን ጥረት ማድረግ ብቻ ነው የሚያስፈልገው" ከማክሰኞ ጀምሮ በኮንጎ ዋና ከተማ ብራዛቪል ውስጥ የተገናኙት ባለሙያዎች ፣የአካባቢ ተወካዮች፤የቴክኒክ እና የፋይናንስ አጋሮች ለመሪዎቹ “የብራዛቪል መግለጫ” በሚል በጉባዔው ማብቂያ ላይ አፅድቀው ለመሪዎቹ የቀርባሉ። "የጊዜያችን ትልቁ ፈተና የደን መጨፍጨፍን ማስቆም ብቻ ሳይሆን ፤ የጨፈጭፍናቸውን መተካት እንዲሁም አዲስ ደን መፍጠር አለመቻላችን ነው" ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0