አሜሪካ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመዳብ ማዕድን ሀብቷን ለቻይና መከላከያ ኩባንያ እንዳይሸጥ ለማድረግ ጥረት ማድጓረን አንድ ዘገባ አመልክቷል።

ሰብስክራይብ
አሜሪካ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ  የመዳብ ማዕድን ሀብቷን ለቻይና መከላከያ ኩባንያ እንዳይሸጥ ለማድረግ ጥረት ማድጓረን አንድ ዘገባ አመልክቷል። የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣናት፤ የቻይና ወሳኝ የተባሉ ማዕድናት የበላይነት ሩጫ ለመግታት ፤የዲ.አር.ሲ መንግስት ማዕድን ኩባንያ ጂካማይን፤የኬማፍ ማዕድን ሃብትን፤የቻይና መንግስት ንብረት ለሆነው ለኖሪኢንኮ ማዕድን ኩባንያ ምርቶቹን እንዳይሽጥ ስታደናቅፍ እንደነበር ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። ጂካማይን መቶሺ የተባለውን ዋና ማዕድን ማውጣት ፕሮጀክት ፈቃዱን በሊዝ ለቻይናው ኬማፍ ኩባንያ አከራይቷል። ኖሪንኮ የኬማፍ ሙቶሺ እና ኢቶይል ማዕድን እና ሌሎች የማዕድን ፈቃዶችን ለማግኘት አቅድ ነበረው። የጂካማይንስ ቦርድ ሽያጩን ውድቅ ያደረገው፤አስቀድሞ ማሳወቅ ስለነበረበት እና ኩባንያውን ለመያዝ የሚደረጉ ማናቸውም ለውጦች ማፅደቅ ስለሚያስፈልጋቸው ነው ብሏል።ነገር ግን ኬማፍ አስቀድሞ ሽያጩን ለጂካማይን እንዳሳወቀው ተናግሯል።ሽያጩ በዲ.አር ኮንጎ ማዕድን ሚኒስትር ፀድቋል ብሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0