ኒጀር ግንኙነቷን ወደነበረበት ለመመለስ እና የነዳጅ መስመር ስራን በድጋሚ ለማስጀመር ከቤኒን ጋር ልትወያይ ነው

ሰብስክራይብ
ኒጀር ግንኙነቷን ወደነበረበት ለመመለስ እና የነዳጅ መስመር ስራን በድጋሚ ለማስጀመር ከቤኒን ጋር ልትወያይ ነው የሀገሪቱ መሪ አብዱራሃማኔ ቲያኒ ሰኔ 17 ከቀድሞ የቤኒን ፕሬዚዳንቶች ቶማስ ቦኒ ያዪ እና ኒሴፎር ሶግሎ ጋር ያደረጉትን ስብሰባ ተከትሎ የመጣ እንደሆነ የሳህል ሀገራት ጥምረት በኤክስ የማህበራዊ ገፅ ላይ ጽፏል። ሆኖም የሁለቱም ሀገራት ባለስልጣናት የስብሰባው ቀን እንዳልተወሰነ ለሮይተርስ ተናግረዋል። በድርድሩ ምክንያት በቻይናው ኩባንያ ፔትሮ ቻይና ተሳትፎ በተገነባው የቧንቧ መስመር ከኒጀር ወደ ቤኔን የሚገባው የነዳጅ አቅርቦት በድጋሚ ሊጀምር ይችላል ተብሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0