የሩዋንዳን የነጻነት ቀን አስመልክቶ ሩሲያ ኪጋሊን "አስተማማኝ አጋር" ስትል አወደሰች

ሰብስክራይብ
የሩዋንዳን የነጻነት ቀን አስመልክቶ ሩሲያ ኪጋሊን "አስተማማኝ አጋር" ስትል አወደሰች በሺዎች የሚቆጠሩ ሩዋንዳውያን በቱትሲዎች ላይ የተፈጸመው የዘር ማጥፋት ያበቃበት እና የሩዋንዳ አርበኞች ጦር ድል የተጎናፀፈበትን ሰኔ 27 ቀን ለመዘከር በአማሆሮ ስታዲየም እንደተሰበሰቡ የአፍሪካዊቷ ሀገር የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዚህ አጋጣሚ የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሊቀመንበር ቫለንቲና ማትቪንኮ በሞስኮ እና በኪጋሊ መካከል ያለውን ትብብር አድንቀዋል። "በተለምዶ ወዳጃዊ እና መተማመን ላይ ለተመሰረተው የሩሲያ-ሩዋንዳ ግንኙነት ዋጋ እንሰጣለን። ሩዋንዳን አስተማማኝ እና የረዥም ጊዜ አጋር አድርገን እንቆጥራለን" ሲሉ ለሩዋንዳ ሴኔት ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ዛቪየር ካሊንዴ በላኩት መልእክት ጽፈዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0