በ2023/24 የግብርና ምርት ዘመን ሩሲያ በዓለም የስንዴ ገበያ ያላት ድርሻ ወደ 28% ማደጉን የሀገሪቱ የሎጂስቲክስ ኩባንያ አስታወቀ

ሰብስክራይብ
በ2023/24 የግብርና ምርት ዘመን ሩሲያ በዓለም የስንዴ ገበያ ያላት ድርሻ ወደ 28% ማደጉን የሀገሪቱ የሎጂስቲክስ ኩባንያ አስታወቀ ሩሲያ 55.4 ሚልየን ቶን ስንዴ ወደ ውጭ የላከች ሲሆን ይህም ከጠቅላላው 200 ሚሊዮን ቶን የዓለም የንግድ መጠን 28% ገደማ እንደሆነ የሩሳግሮትራንስ የሎጂስቲክስ ኩባንያ የቅድሚያ ትንተና አመልክቷል። ሀገሪቱ ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት 34 ሚሊዮን ቶን የስንዴ ኤክስፖርት እንዲሁም ከካናዳ 23.5 ሚሊዮን ቶን፣ ከአውስትራሊያ 20.5 ሚሊዮን ቶን እና ከዩናይትድ ስቴትስ 19.6 ሚሊዮን ቶን በመላቅ ወደ ውጪ መላክ ችላለች። በሪፖርቱ መሠረት የሩሲያን ስንዴ የሚገዙ ሦስቱ ዋና ዋና ሀገራት ከታች የተዘረዘሩት ናቸው፦ 🟠 ግብፅ (8.6 ሚሊዮን ቶን) 🟠 ቱርክ (7 ሚሊዮን ቶን) 🟠 ባንግላዴሽ (3.8 ሚሊዮን ቶን) ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0