ደቡብ አፍሪካ፡ የቀድሞ ተቃዋሚ ፓርቲ ከ30 የሚኒስትሮች ቦታ 6ቱን እንደሚያገኝ ሲነገር፤ ቀሪውን የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ እንደሚይዝ ተነግሯል

ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ፡ የቀድሞ ተቃዋሚ ፓርቲ ከ30  የሚኒስትሮች ቦታ 6ቱን እንደሚያገኝ ሲነገር፤ ቀሪውን የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ እንደሚይዝ ተነግሯል ኒውስ 24 የተባለ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን  እንደዘገበው የዴሞክራቲክ ህብረት ተወካዮች የሚከተሉትን የሚኒስትር ቦታ ይይዛሉ 🟠 ግብርና፣መሬት ሪፎርምና ገጠር ልማት 🟠 መሠረታዊ ትምህርት 🟠 መገናኛ እና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች 🟠 አካባቢ፣ደን እና አሳ ልማት 🟠 የቤት ጉዳይ 🟠 የህዝብ ስራዎች እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር መስሪያ ቤቶችን ይመራሉ። በተጨማሪም  የዴሞክራቲክ ሕብረት አባላት፤የገንዘብና ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ውድድር ሚኒስቴር እንዲሁም አዲስ የተቋቋመውን የኢነርጂና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴርን ጨምሮ በድምሩ ስድስት የምክትል ሚኒስትር ቦታዎችን እንደሚይዙ ተነግሯል። ከ1994-2024 ብቸኛ ገዥ ፓርቲ ሆኖ የቆየው የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ በበኩሉ የጸጥታውን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን እንዲሁም ሌሎች ቁልፍ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ቦታዎችን ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራል። በአጠቃላይ አዲሱ መንግስት 10 የፓርላማ መቀመጫ ያገኙ ፓርቲዎችን ያካተተ ቢሆንም ፤ የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ እና ዴሞክራቲስ ሕብረት ብቻ በሚኒስትሮች የስራ መደቦች ላይ ድርድር አድርገዋል ሲል ኒውስ 24  ዘግቧል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0