ደቡብ አፍሪካ ጥምር መንግስት ካቋቋመች በኋላ ካቢኔ ልታዋቅር ከጫፍ ደርሳለች መድረሷን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ ጥምር መንግስት ካቋቋመች በኋላ ካቢኔ ልታዋቅር ከጫፍ ደርሳለች መድረሷን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በርካታ የዜና አውታሮች እንደዘገቡት በጥምረቱ ውስጥ ያሉት ሁለቱ ዋና ዋና ፓርቲዎች ፤የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ እና ዴሞክራቲክ አሊያንስ (የቀድሞው ዋና ተቃዋሚ ፓርቲ) በአብዛኛዎቹ ነጥቦች ላይ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።ይህም የሆነው ፤ ዴሞክራቲክ አሊያንስ  ፓርቲ ንግድን ሚኒስትር ቦታን የመውሰድ ሀሳቡን ከተወ በኋላ እንደሆነ ተነግሯል። የዴሞክራቲክ አሊያንስ  ፓርቲ ከፍተኛ አባል ሔለን ዚሌ “የሳምንቱ መጨረሻ ከማብቃቱ በፊት ተስማምተናል ብለን እንደምናውጅ ተስፋ እናደርጋለን” ስትል ተናግራለች። ከዚህ ቀደም አሥር የደቡብ አፍሪካ የፖለቲካ ፓርቲዎች የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለመመሥረት መስማማታቸው ይታወሳል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0