የሰኔ 22 ምሽት ዋናዋና የዓለም ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የሰኔ 22 ምሽት ዋናዋና የዓለም ዜናዎች 🟠 በቦጉን-ጎሮዶክ  እና በዚቦሮቭካ እንዲሁም በኔቻዬቭካ ገጠራማ ሰፈሮች መካከል በሚገኘው የሩሲያ ቤልጎሮድ ግዛት መንደሮች ላይ በደረሰ የድሮን ጥቃት ሶስት ንፁሀን ዜጎች መቁሰላቸውን የገዛቱ አስተዳዳሪ ቭያቼስላቭ ግላድኮቭ ተናግረዋል። 🟠 በቤልግሬድ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኑ በመዘጋቱ የሽብር ጥቃት የደረሰበት አንድም ሰው እንደሌለ ተገልጿል፤ሁኔታውን ግን በመርመር ላይ መሆናቸው ተገልጿል። 🟠 በእስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባለፉት 24 ሰዓታት ባደረሰችው 3 ጥቃቶች ፤40 ሰዎች ሲሞቱ 224 ሰዎች ደግሞ መቁሰራቸውን የአከባቢው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልፆጿል። ተጎጂዎቹ ወደ ሆስፒታል መግባታቸውንም ተገልጿል። 🟠 የቱርክ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው ሪፐብሊካን ፒፕልስ ፓርቲ መሪ ኦዝጉር ኦዝል ከአንድ ወር ተኩል በኋላ ከሶሪያው ፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድ ጋር በሶሪያ እንደሚገናኙ ተናግረዋል። 🟠 በጃፓን ኦኪናዋ ግዛት በሚገኘው አሜሪካ ካዴና ጦር ሰፈር ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። የተቃውሞ ሰልፉ የተካሄደው በጦር ሰፈሩ ያሉ የአሜሪካ ወታደሮች ተሳትፈውበታል በተባለበት ተደጋጋሚ ፆታዊ ትንኮሳ ሳቢያ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0