ለዩክሬን የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ እ.ኤ.

ሰብስክራይብ
ለዩክሬን የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ እ.ኤ.አ ከየካቲት 2022 ጀምሮ በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱ ተነገረ በ 2024 የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ወርሃዊ አማካኝ ድጋፉ ወደ 1.9 ቢሊዮን ዩሮ (2 ቢሊዮን ዶላር)ዝቅ ብሏል። የዩክሬን ፋይናንስ ሚኒስቴር መረጃ መሠረት አድርጎ በስፑትኒክ የሰራው ትንታኔ እንደሚያሳየው ኪየቭ በግንቦት ወር ምንም ገንዘብ እንዳላገኘ አመልክቷል። በ 2022 የዩክሬን የተደረገላት ድጋፍ፡- ከ17 ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት በአማካይ በወር 2.9 ቢሊዮን ዩሮ ከዩናይትድ ስቴትስ የ11.4 ቢሊዮን ዩሮ ከፍተኛ ድጋፍ ተደርጎላታል። የአውሮፓ ህብረት 7.6 ቢሊዮን ዩሮ ካናዳ 1.8 ቢሊዮን ዩሮ በ2023፡- 13 ሀገራት እና የአውሮፓ ህብረት ለዩክሬን በየወሩ አማካኝ 3 ቢሊዮን ዩሮ (በአጠቃላይ 18.1 ቢሊየን ከአውሮፓ ህብረት) ድጋፍ አግኝታለት። አሜሪካ በ10.1 ቢሊዮን ዩሮ ድጋፍ በመስጠት በሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ ድጋፍ አድርጋለች። ጃፓን 3.4 ቢሊዮን ዩሮ ድጋፍ ሰጥታለች። እ.ኤ.አ በ 2024 ኪየቭ የገንዘብ ድጋፍ ከሚከተሉት Uገራት አግኝታለች የአውሮፓ ህብረት ካናዳ ጃፓን ኖርዌይ ስፔን ዩናይትድ ኪንግደም። ወርሃዊ ድጋፉ ወደ 1.9 ቢሊዮን ዩሮ ወርዷል። ቀደም ሲል ባለሙያዎች ለስፑትኒክ እንዳብራሩት የምዕራባውያን መራጮች ቀስ በቀስ በዩክሬን ቀውስ እየሰለቹ እና መንግስቶቻቸው ለኪየቭ አገዛዝ ተጨማሪ እርዳታ ሲልኩ ማየት አይፈልጉም ብለዋል። ዜናዎቻችንን በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ያጋሩ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0