ፈረንሳይ በጦር ሃይል አደረጃጀቷ ውስጥ የአፍሪካ እዝ በሚል የጦር ሃይል ፈጥራለች።

ሰብስክራይብ
ፈረንሳይ በጦር ሃይል አደረጃጀቷ ውስጥ የአፍሪካ እዝ በሚል የጦር ሃይል ፈጥራለች። "ብሪጋዴር ጄኔራል ፓስካል ኢያኒ የአፍሪካ እዝ ዋና አዛዥ ሆነው ተሹመዋል"ሲል መንግስት ሃሙስ እለት ወታደራዊ ሹመቶች ላይ ባወጣው አዋጅ አስታውቋል፤ኢያኒ እ.አ.አ ከነሀሴ 1 ጀምሮ ላይ እዙን እንዳሚመሩ ተናግሯል። የአፍሪካ እዝ ለመመሥረት በፓሪስ ውይይት ሲደረግ ፈረንሳይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ወታደሮቿን ቁጥር በመቀነስ ላይ መሆኑ እንደ ድክመት መሸፈኛ ተቆጥሯል። የሀገሪቱ መንግስት በምዕራብ እና በመካከለኛው አፍሪካ ያለውን ጦር ሀይል ለመቀነስ ማቀዱን የዘገበው ኤ ኤፍ ፒ ይህም በእነዚህ አካባቢ የተቀዛቀዘውን አጋርነት ውጤት መሆኑን ዘግቧል። ፓሪስ በጋቦን እና በሴኔጋል ወደ 100 የሚጠጉ ወታደሮችን ለማሰማራት አቅዳለች ፣ይህም ቀደም ሲል በእያንዳንዱ ሀገር ከተሰማሩት 350 የወታደሮች ቁጥር ጋር ሲኒያየር ቁጥሩ ዝቅ ብሏል።በኮትዲቯር ያለው የወታደር ቁጥር ከ600 ወደ 100 የሚቀንስ ሲሆን በቻድ ደግሞ ፈረንሳይ ወደ 300 የሚጠጉ ወታደሮችን ታሰማራለች፣ ይህም ቀደም ሲል ከነበረው 1,000 ጋር ሲነጻጸር ቁጥሩ አነስተኛ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0