ሰኔ 20 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች
🟠 የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ራማፎሳ የተቃዋሚ ፓርቲ ዲሞክራቲክ አሊያንስ አመራሮች የብሄራዊ አንድነት መንግስት ምስረታን አደጋ ላይ ጥለዋል ሲሉ መክሰሳቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
🟠 በምዕራብ ኬንያ በምትገኝ ሆማ ቤይ ከተማ ቢያንስ 11 ሰዎች መቁሰላቸውን ኔሽን ጋዜጣ ዘግቧል። የተወሰኑ ሰዎች በተተኮሰ ጥይት መቁሰላቸው ተዘግቧል።
🟠 በቦሊቪያ የህግ አስከባሪ አካላት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገዋል ያሏቸው ቢያንስ 10 ወታደራዊ አባላትን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የቦሊቪያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ካርሎስ ዴል ካስቲሎ ዴል ካርፒዮ ሪፖርት አድርገዋል።
🟠 23 ህጻናትን ጨምሮ 66 ሰዎች በሩሲያ ሴቫስቶፖል ከተማ በተፈፀመ ጥቃት ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸውን የሩሲያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ።
🟠 የአውሮፓ ህብረት እና ዩክሬን የጋራ የደህንነት ቃል ኪዳኖችን ተፈራርመዋል።
🟠 የቱርክ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን በዩክሬን ግጭት ዙሪያ ሩሲያን ያላሳተፈ የሰላም ሃሳብ ውጤት አያመጣም ብለዋል።
🟠 ኔቶ የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ እና በቤላሩስ ድንበር ለመከላከያ መስመር ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደማይቃወም ዋና ጸሃፊ ስቶልተንበርግ ተናግረዋል ።
🟠 የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ፤ባርዴላ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ ወታደሮቻቸውን ወደ ዩክሬን መላክ አይችሉም ሲሉ ማሪን ለፔን ለ ቴሌግራም ጋዜጣ ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ሰኔ 20 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች
ሰኔ 20 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች
Sputnik አፍሪካ
ሰኔ 20 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች 🟠 የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ራማፎሳ የተቃዋሚ ፓርቲ ዲሞክራቲክ አሊያንስ አመራሮች የብሄራዊ አንድነት መንግስት ምስረታን አደጋ ላይ ጥለዋል ሲሉ መክሰሳቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። 🟠... 27.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-27T20:18+0300
2024-06-27T20:18+0300
2024-06-27T20:40+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий