የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ብጥብጥ በቀሰቀሰው የግብር ጭማሪ ህግ ላይ እንደማይፈርሙ ተናገሩ
ማክሰኞ በተፈጠረው አለመረጋጋት ለተገደሉት እና ለተጎዱ ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝተዋል።
በህጉ ማሻሻያዎች ላይ ከሀገሪቱ የወጣት ተወካዮች ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
ሁሉም ፓርቲዎች እና የፖለቲካ ሃይሎች በማሻሻያው ላይ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
ሩቶ በሀገሪቱ እድገት ዙርያ ፍላጎት ያላቸው ሁሉ ሕግ የማውጣት ሂደቱ ላይ የሕግ የበላይነት እና የኬንያን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት በማክበር እንዲሳተፉ ጠይቀዋል።
በማክሰኞው ሁከት በድምሩ 6 ወጣቶች ህይወታቸውን ማጣታቸውን የገለፁት ሩቶ “ከዚህ በኋላ ከሕግ ውጭ የሚፈጸሙ ግድያዎች እንደማይኖሩም” ቃል ገብተዋል።
የሀገሪቱን በጀት በግብር ማሟላት ኬንያ ነፃ የጤና እና የትምህርት ስርዓት እንዲሁም ግብርናን እንድታሳድግ ያስችላታል ሲሉ ፕሬዝዳንት ሩቶ ተናግረዋል።
ማክሰኞ ወደ 214 የሚጠጉ ኬንያውያን ከፖሊስ ጋር በተደረገው “ፍጥጫ” ውስጥ ተሳታፊ እንደነበሩም አንስተዋል።
አንድ በድንገተኛ ክፍል ውስጥ የሚገኝ ተሳታፊን ጨምሮ 14 ያህሉ አሁንም በሆስፒታሎች ውስጥ እንደሚገኙ አክለዋል።
ኬንያ "የሌሎች ሀገራት ፋብሪካዎች መደብር ሆና መቀጠል አትችልም" ሲሉም ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ብጥብጥ በቀሰቀሰው የግብር ጭማሪ ህግ ላይ እንደማይፈርሙ ተናገሩ
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ብጥብጥ በቀሰቀሰው የግብር ጭማሪ ህግ ላይ እንደማይፈርሙ ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ብጥብጥ በቀሰቀሰው የግብር ጭማሪ ህግ ላይ እንደማይፈርሙ ተናገሩ ማክሰኞ በተፈጠረው አለመረጋጋት ለተገደሉት እና ለተጎዱ ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝተዋል። በህጉ ማሻሻያዎች ላይ ከሀገሪቱ የወጣት ተወካዮች ጋር ለመወያየት... 26.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-26T19:43+0300
2024-06-26T19:43+0300
2024-06-26T20:20+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ብጥብጥ በቀሰቀሰው የግብር ጭማሪ ህግ ላይ እንደማይፈርሙ ተናገሩ
19:43 26.06.2024 (የተሻሻለ: 20:20 26.06.2024)
ሰብስክራይብ