የኬንያ ቀይ መስቀል የተቃውሞ ሰልፈኞች በአምቡላንሱ እና ሰራተኞቹ ላይ ጥቃት አንዳደረሱ ገለፀ

ሰብስክራይብ
የኬንያ ቀይ መስቀል የተቃውሞ ሰልፈኞች በአምቡላንሱ እና ሰራተኞቹ ላይ ጥቃት አንዳደረሱ ገለፀ "ተሽከርካሪዎቻችን ላይ ጥቃት ደርሷል። ሰራተኞች እና በጎ ፈቃደኞች ላይ ጉዳት ደርሷል። ከተጎጂዎች ውጪ ከማንም ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለንም ወይም ማንንም አናጓጉዝም። ያልተረጋገጡ ወሬዎች መቆም አለባቸው። ያለ ሰራተኞቻችን እና በጎ ፍቃደኞቻችን ደህንነት እና የመድረስ አቅም የህይወት አድን ስራዎቻችንን ማቅረብ አንችልም። የሰብአዊ ስራዎቻችንን ያለምንም እንቅፋት እንድናካሄድ ፍቃድ ያስፈልገናል” ሲል የኬንያ ቀይ መስቀል በኤክስ የትስስር ገፁ ላይ ተናግሯል። ሰራተኞቻቸን እና በጎ ፍቃደኞቻችን “ለተጎዱ ሰዎች ወሳኝ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ሕይወታቸውን አደጋ ላይ እየጣሉ” ሳለ “የፓርላማ አባላትን ይዘው እየወጡ ነው ተብለው መከሰሳቸው ተገቢ አይደለም” ሲልም አክሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0