የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪው በጀት ዓመት የ8.

ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪው በጀት ዓመት የ8.3% ዕድገት እንዲያስመዘግብ ይጠበቃል ተባለ የኢትዮጵያ ፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ በ2016 የኢትዮጵያ በጀት ዓመት 10 ወራት በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶች በዓመቱ መጨረሻ የ7.9% የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ አመላካች ናቸው ብለዋል። በ2017 በጀት ዓመት ጥቅል ሀገራዊ ኢኮኖሚው የ8.3% ዕድገት እንዲያስመዘግብ መታቀዱንም አስረድተዋል። ግቡን ለማሳካት በግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና በዲጅታል ዘርፍ ቅንጅታዊ አሰራርን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል። የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት የአሰራር ማሻሻያን አጠናክሮ መቀጠልና የገበያ መሰረተ ልማቶችን የማዘመን ስራ በስፋት ይተገበራል ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0