ከሀጅ ጋር በተገናኘ ሞት ምክንያት ግብፅ የ16 የቱሪዝም ኩባንያዎችን የስራ ፍቃድ በመሰረዝ ጉዳዩን ለአቃቤ ህግ ላከች

ሰብስክራይብ
ከሀጅ ጋር በተገናኘ ሞት ምክንያት ግብፅ የ16 የቱሪዝም ኩባንያዎችን የስራ ፍቃድ በመሰረዝ ጉዳዩን ለአቃቤ ህግ ላከች የሀገሪቱ የህክምና እና የደህንነት ምንጮች እንደገለፁት በዚህ ዓመት ወደ መካ በተደረገው የሃጅ ጉዞ በአጠቃላይ 530 ግብፃውያን በከፍተኛ ሙቀት ህይወታቸውን አጥተዋል። ግብፅ ሞቱን የሚመረምር የቀውስ ክፍል ሐሙስ እለት አቋቁማለች። የሟቾችን ጉዞ ያመቻቹት የቱሪዝም ኩባንያዎች የህክምና እርዳታን ጨምሮ ምንም አይነት አገልግሎት አልሰጡም። ኤጀንሲዎቹ ተጓዦቹ በመካ የሐይማኖት ስነስርዓት መካፈል ከሚያስችላቸው የሃጅ ቪዛ ይልቅ በጉብኝት ቪዛ ወደ ሳዑዲ አረብያ በመላካቸው ተተችተዋል። በግል ቪዛ የተጓዙት የሃጅ ተጓዦች የህክምና አገልግሎት አላገኙም። ህይወታቸውን ያጡት የሐይማኖት ተጓዦች መካ ለመድረስ እና እስራትና መባረርን ፍራቻ በረሃ በእግር ማቋራረጥ እንደነበረባቸው ታውቋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0