#አጫጭርዜና

ሰብስክራይብ
#አጫጭርዜና የስፑትኒክ ኢትዮጵያ ትኩስ ዜናዎችን ይከታተሉ፦ 🟠 የክራይሚያ ልሳነ ምድር ትልቋ ከተማ በሆነችው ሴቫስቶፖል በደረሰው የዩክሬን ሚሳኤል ጥቃት የሟቾች ቁጥር አምስት መድረሱን ገዥው ሚካሂል ራዝቮዛይቭ ገለፁ። 🟠 በሴቫስቶፖል ሰላማዊ ዜጎች ላይ ለደረሰው የታቀደ የሚሳኤል ጥቃት ተጠያቂነት በዋነኝነት መሳሪያዎቹን ባቀረበችው ዋሽንግተን እንዲሁም የጥቃቱ መነሻ በሆነው የኪዬቭ አገዛዝ ላይ እንደሚያርፍ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል። 🟠 የታላቁ የአርበኞች ጦርነት ትልቁ እና ስኬታማ ስትራቴጂክ ዘመቻ የባግሬሽን ጥቃት ከ80 ዓመት በፊት በዛሬ ቀን ነው የተጀመረው። 🟠 ሩዋንዳ በሚቀጥለው ወር ለሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ እና የፓርላማ ምርጫ ቅስቀሳ ጀምራለች። 🟠 በዶንባስ ውስጥ የሚያገለግል ፈረንሳዊው የምዕራባዊ እና የሩሲያ ወታደራዊ መሳሪያዎችን አወዳድሯል። 🟠 የማሊ የሽግግር ፕሬዝዳንት አሲሚ ጎይታ ፈረንሳይ የማሊን ኢኮኖሚ ለመጉዳት ሀሰተኛ ሴኤፍኤ ፍራንክ ኖቶችን ታትማለች ሲሉ ከሰሱ። 🟠 10 የፖለቲካ ፓርቲዎች የደቡብ አፍሪካ ጥምር መንግስትን ሊቀላቀሉ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0