ትራምፕ የአሜሪካን ወታደሮች የዩክሬን መሬትን እንደማይረግጡ ቃል ገብተዋል

ሰብስክራይብ
ትራምፕ የአሜሪካን ወታደሮች የዩክሬን መሬትን እንደማይረግጡ ቃል ገብተዋል የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጪው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ ዩክሬንን ለመርዳት የአሜሪካ ወታደሮችን እንደማይልኩ ቃል ገብተዋል። ትራምፕ ከዩቲዩብ ቻናል ኦል ኢን ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ምንም ይሁን ምን የአሜሪካን ወታደሮች የዩክሬን መሬት እንደማይረግጡ "ዋስትና እሰጣለሁ፤ አላደርገውም"ብለዋል። በተጨማሪም የዩክሬን ኔቶ ለመቀላቀል እያደረገች ያለችው ንግግር ለአሁኑ ግጭት መንስኤ መሆኑን ትራምፕ ጠቁመዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0