ሲሪል ራማፎሳ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለ መሃላ በመፈጸም ሁለተኛውን የአምስት አመት የስልጣን ዘመናቸውን ጀመሩ።

ሰብስክራይብ
ሲሪል ራማፎሳ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለ መሃላ በመፈጸም ሁለተኛውን የአምስት አመት የስልጣን ዘመናቸውን ጀመሩ። "እኔ ማታሜላ ሲሪል ራማፎሳ ለደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ታማኝ በመሆን፤ ህገ-መንግስቱን እና የሪፐብሊኩን ህግጋት ሁሉ በማክበር ፣ በመጠበቅ እና በማስከበር ቃል እገባለሁ ።"ሲሉ በሀገሪቱ ዋና ዳኛ ሬይመንድ ዞንዶ አማካኝነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል። በቃለ መሃላው ሥነ ሥርዓት ላይ ከ18 ሀገራት የተውጣጡ የሀገር መሪዎች፤ በተለይም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል። ሩሲያም በደቡብ አፍሪካ የሃገሪቱ አምባሳደር በሆኑት ኢሊያ ሮጋቼቭ ተወክላለች። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0