የሰኔ 11 የቀትር ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች፡-

ሰብስክራይብ
የሰኔ 11 የቀትር ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች፡- 🟠 ሩሲያ የአፍሪካ ህፃናትን ለመርዳት የሰብዓዊ ተልእኮዋን እንደምታሰፋ የሩሲያ የህፃናት መብት ኮሚሽነር ማሪያ ልቮቫ-ቤሎቫ አስታወቁ። 🟠 ምዕራባውያን በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን ቦታ ሲያጡ ሩሲያ በአህጉሪቱ ያላትን አቋም እያጠናከረች ነው ሲሉ የአውሮፓ ህብረት ዋና አዛዥ ሌተናንት ጄኔራል ሚቺኤል ቫን ደር ላን ተናግረዋል። 🟠 የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ወደ ሰሜን ኮሪያ ከመጓዛቸው በፊት ሰሜን ኮሪያ ጋዜጣ "ሮዶንግ ሲንሙን" እና በክሬምሊን ድረ-ገጽ ላይ አምድ አሳተሙ፡፡ 🟠 የጠላፊው ቡድን ራኤችዲት ከ1,200 በላይ የዩክሬን ሰው አልባ አቪዬሽን ኦፕሬተሮች ላይ መረጃ አውጥቷል። መረጃው የጦር ክፍሉን አጠቃላይ መዋቅር የሚያሳይ ሲሆን እንደ የሩስያ የምርመራ ኮሚቴ የጦር ክፍሉ በሩሲያ የካሉጋ፣ ራያዛን እና ሳራቶቭ ክልሎች አየር ማረፊያዎች ላይ የሞት አደጋን ባደረሰ ጥቃት ተሳታፊ ነው፡፡ 🟠 የአውሮፓ ህብረት ሀገራት መሪዎች ቮን ደር ሌየንን ለሁለተኛ ጊዜ የአውሮፓ ኮሚሽን መሪ አድርጎ ለመሾም ስምምነት ላይ አልደረሱም ሲሉ የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ተናግረዋል ። 🟠 የምዕራቡ ዓለም የሩሲያ ንብረት ወረሳ ዓለም አቀፍ ህግን የሚጥስ እና የዓለም መገበያያዎች እና ተቋማት ላይ እምነት የሚያሳጣ ነው ሲሉ የማሊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለፁ። 🟠 የፓስፊክ የባህር ጦር 40 የሚጠጉ መርከቦችን፣ ጀልባዎችን እና የድጋፍ መርከቦችን እንዲሁም ወደ 20 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና የባህር ኃይል ሄሊኮፕተሮችን በማካተት በሩቅ ምስራቅ ልምምዶችን ማድረግ ጀምሯል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0