ኢራቅ እና ዮርዳኖስ በስዊዘርላንድ አስተናጋጅነት በተካሄደው የዩክሬን ጉባኤ የመጨረሻ የጋራ መግለጫ ፈራሚዎች ዝርዝር ውስጥ "በቅንጅት ችግር" ምክንያት ሊካተቱ እንደቻሉ የስዊዘርላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቫለንቲን ክሊቫዝ ሰኞ እለት ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ሰብስክራይብ
ኢራቅ እና ዮርዳኖስ በስዊዘርላንድ አስተናጋጅነት በተካሄደው የዩክሬን ጉባኤ የመጨረሻ የጋራ መግለጫ ፈራሚዎች ዝርዝር ውስጥ "በቅንጅት ችግር" ምክንያት ሊካተቱ እንደቻሉ የስዊዘርላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቫለንቲን ክሊቫዝ ሰኞ እለት ለስፑትኒክ ተናግረዋል። "በእንደዚህ አይነት ሁኔታች እያንዳንዱ በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፍ የልዑካን ቡድን አስቀድሞ መግለጫውን ይቀበላል፤ ፊርማውን የሚቃወም ከሆነ ለአስተናጋጅ ሀገር [ስዊዘርላንድ] ማሳወቅ አለበት፡፡ ኢራቅ እና ዮርዳኖስ በመግለጫው ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ባለመግለፃቸው የፈራሚ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ተካተዋል፡፡ የመጨረሻው መግለጫ ከወጣ በኋላ ከፈራሚዎች ዝርዝር ውስጥ እንዲነሱ በመጠያቃቸው ሊነሱ ችለዋል፡፡ የቅንጅት ችግር ብቻ ነው” ብለዋል ቃል አቀባዩ፡፡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0