በርካታ ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል ይፈልጋሉ ሲሉ የሩስያ የፀጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ገለፁ

ሰብስክራይብ
በርካታ ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል ይፈልጋሉ ሲሉ የሩስያ የፀጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ገለፁ ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ “ሌሎች ሀገሮች ብሪክስን ለመቀላቀል እየፈለጉ ነው። ከክልላችን የመጡትን ጨምሮ- ታይላንድ፣ ቬትናም እና ሌሎች በርካታ ሀገሮች አሉ” ሲሉ ብሪክስ አዲስ የብዙኃን የዓለም ሥርዓት ግንባታ ላይ ስለሚኖረው ሚና በሚያተኩረው የዩናይትድ ሩሲያ ፓርቲ ዓለም አቀፍ የፓርቲዎች ፎረም ምልአተ ጉባኤ ላይ ተናግረዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባለፈው አርብ ሩሲያ በርካታ ሀገራት ብሪክስ ውስጥ የመካተት ፍላጎት እንዳላቸው እየተገነዘበች መሆኑን እና አዳዲስ ተሳታፊዎችን ያለችግር ለማካተት የሚቻልበትን መንገድ እንደምታመቻች ገልፀው የህብረቱ አቅም የብዙኃን የዓለም ሥርዓትን ከሚቆጣጠሩ ዋና ተቋማት አንዱ እንዲሆን ያስችለዋል ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0