የሰኔ 10 የቀትር ዋና ዋና የዓለም ጉዳዮች፡-
🟠 በቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ የሚመራው ኡምኮንቶ ዌ ሲዝዊ ፓርቲ የብሄራዊ አንድነት መንግስትን ምስረታን እንደማይቀላቀል እና ፓርላማ ውስጥ ተቃዋሚዎችን እንደሚመራ ገልጿል።
🟠 በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ልዑክ የወታደሮች መውጣት "የፀጥታ ክፍተት" እንደማይፈጥር ለሀገሪቱ ነዋሪዎች አረጋገጡ። በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልእኮ (አትሚስ) በሶስተኛው ምዕራፍ ወታደራዊ ቅነሳ የባሪሬ ጦር ሰፈርን ለሶማሊያ የጸጥታ ሃይሎች አስረክቧል።
🟠 የሩሲያ የፀጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ በርካታ ሀገራት የብሪክስ ቡድንን ለመቀላቀል እንደሚሹ ገለፁ።
🟠 በሩሲያ ቤልጎሮድ፣ ቮሮኔዝ እና ሊፕትስክ ክልሎች ላይ ስድስት ድሮኖች እንደወደሙ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ዘግቧል።
🟠 የኔቶ አባል ሀገራት የሕብረቱን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ወደ ዝግጁነት ደረጃ ለማምጣት ምክክር እያደረጉ እንደሆነ ዋና ፀሐፊው የንስ ስቶልተንበርግ ገለፁ።
🟠 አደንዛዥ ዕፅ በማዘዋወር፣ በስልክ ስርቆት፣ በታጠቁ ጥቃቶች እና በነፍስ ግድያ ጥፋተኛ የተባሉ እስረኞችን ጨምሮ ከ2,750 የሚበልጡ እስረኞች ከዩክሬን እስር ቤቶች ተለቀው በዩክሬን ጦር ኃይሎች ውስጥ እንዲያገለግሉ ተላኩ።
🟠 የምዕራባውያን ሀገራት ንብረቶቿን ለመውረስ ከወሰኑ ሩሲያ መብቷን ለማስጠበቅ "በእጇ ያሉ ሁሉንም መሳሪያዎች" ትጠቀማለች ሲሉ በመንግስታቱ ድርጅት የሩስያ ተወካይ ቫሲሊ ኔቤንዝያ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የሰኔ 10 የቀትር ዋና ዋና የዓለም ጉዳዮች፡-
የሰኔ 10 የቀትር ዋና ዋና የዓለም ጉዳዮች፡-
Sputnik አፍሪካ
የሰኔ 10 የቀትር ዋና ዋና የዓለም ጉዳዮች፡- 🟠 በቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ የሚመራው ኡምኮንቶ ዌ ሲዝዊ ፓርቲ የብሄራዊ አንድነት መንግስትን ምስረታን እንደማይቀላቀል እና ፓርላማ ውስጥ ተቃዋሚዎችን እንደሚመራ ገልጿል። 🟠 በሶማሊያ... 17.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-17T12:15+0300
2024-06-17T12:15+0300
2024-06-17T12:40+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий