የሩስያ ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ለሀገሪቱ አስጎብኚዎች የታንዛኒያን አዳዲስ የቱሪስት መስመሮችን እንዳስተዋወቀ እና የቻርተር በረራዎችን ለማስጀመር መሰረት እንደሚሆን ገለፀ

ሰብስክራይብ
የሩስያ ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ለሀገሪቱ አስጎብኚዎች የታንዛኒያን አዳዲስ የቱሪስት መስመሮችን እንዳስተዋወቀ እና የቻርተር በረራዎችን ለማስጀመር መሰረት እንደሚሆን ገለፀ "በሀገሮቻችን መካከል ያለው የቱሪዝም አቅም ከፍተኛ ነው፣ ነገር ግን እራሳችንን የበለጠ በንቃት ማስተዋወቅ እና ለሩስያውያንም አዲስ የመዝናኛ ደረጃ ተመጣጣኝ በሆኑ የቱሪስት ምርቶች መፍጠር አስፈላጊ ነው" ማለታቸውን የባለብዙ ወገን ኢኮኖሚያዊ ትብብር እና ልዩ ፕሮጀክቶች ክፍል ዳይሬክተሩን ኒኪታ ኮንድራቲቭን ጠቅሶ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ ሩስያውያን ወደ አፍሪካ ሀገራት ለመጓዝ ፍቃደኛ ቢሆኑም እስካሁን በሩስያ ገበያ በስፋት የሚተዋወቁትን እንደ ግብፅ፣ ቱኒዚያ፣ ሞሮኮ ወይም ሲሼልስ ያሉ መዳረሻዎችን ይመርጣሉ። በ2023 የሩስያ ቱሪስቶች 1.3 ሚልየን ጉዞዎችን ወደ አፍሪካ ሀገራት አድርገዋል ይህም ከ2022 1.4 ግዜ ጭማሬ አሳይቷል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0