በተመድ የሩስያ ልዑክ የፀጥታው ምክር ቤት ሱዳን ላይ ያቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሀሳብ ከእውነታ የራቀ እና የሱዳናውያንን "መርህ ተኮር አስተያየቶች" ችላ ያለ ብሎታል
በተባበሩት መንግሥታት የሩስያ ምክትል ቋሚ ተወካይ አና ኢቪስቲግኒቫ በረቂቅ ሰነዱ ድምፅ አሰጣጥ ላይ ስምምነት ላይ መድረስ እንደማይቻል ተናግረዋል።
በፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ወቅት "የቀረበው የውሳኔ ሃሳብ በሱዳን ያለውን ውስብስብ ሁኔታ ለመፍታት የሚያስችል ምንም አይነት ተጨባጭ ሀሳቦችን አልያዘም። ሰነዱ የሱዳንን አስተያየት ግንዛቤ ውስጥ ያልከተተ እና በተደረሱ ስምምነቶች ላይ የተመሰረተ አይደለም" ሲሉ አብራርተዋል።
ሐሙስ እለት የተመድ የፀጥታ ምክር ቤት በዩናይትድ ኪንግደም የቀረበውን እና ከሌሎች ጉዳዮች በተጨማሪ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በምዕራብ ሱዳን በምትገኘው የአል ፋሸር ከተማ እያካሄደ ያለውን ከበባ እንዲያቆም እና በከተማው ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ የሚያቀርበውን ምክረ ሀሳብ ተቀብሏል። የውሳኔ ሃሳቡን 14 ሀገራት ሲደግፉት ሩስያ ድምፅ ከመስጠት ተቆጥባለች።
ኢቪስቲግኒቫ ሩስያ የፀጥታው ምክር ቤት "አባል ሀገራት" የሱዳንን ሰብዓዊ ተደራሽነት ለማረጋገጥ ከመልካም ዓላማዎች ጀርባ መደበቅ እንዲያቆሙ ትጠይቃለች ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
በተመድ የሩስያ ልዑክ የፀጥታው ምክር ቤት ሱዳን ላይ ያቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሀሳብ ከእውነታ የራቀ እና የሱዳናውያንን "መርህ ተኮር አስተያየቶች" ችላ ያለ ብሎታል
በተመድ የሩስያ ልዑክ የፀጥታው ምክር ቤት ሱዳን ላይ ያቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሀሳብ ከእውነታ የራቀ እና የሱዳናውያንን "መርህ ተኮር አስተያየቶች" ችላ ያለ ብሎታል
Sputnik አፍሪካ
በተመድ የሩስያ ልዑክ የፀጥታው ምክር ቤት ሱዳን ላይ ያቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሀሳብ ከእውነታ የራቀ እና የሱዳናውያንን "መርህ ተኮር አስተያየቶች" ችላ ያለ ብሎታል በተባበሩት መንግሥታት የሩስያ ምክትል ቋሚ ተወካይ አና ኢቪስቲግኒቫ በረቂቅ ሰነዱ ድምፅ... 15.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-15T10:37+0300
2024-06-15T10:37+0300
2024-06-15T12:20+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
በተመድ የሩስያ ልዑክ የፀጥታው ምክር ቤት ሱዳን ላይ ያቀረበውን ረቂቅ ምክረ ሀሳብ ከእውነታ የራቀ እና የሱዳናውያንን "መርህ ተኮር አስተያየቶች" ችላ ያለ ብሎታል
10:37 15.06.2024 (የተሻሻለ: 12:20 15.06.2024)
ሰብስክራይብ