ሁለት የፈረንሳይ ዜጎች በባንግዌ በቁጥጥር ስር ውለው የጦር መሳሪያዎች ከቤታቸው ተወስደዋል

ሰብስክራይብ
ሁለት የፈረንሳይ ዜጎች በባንግዌ በቁጥጥር ስር ውለው የጦር መሳሪያዎች ከቤታቸው ተወስደዋል የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት ተጠርጣሪዎቹ ከታጣቂ ቡድን መሪዎች እና ከተወሰኑ የብሄራዊ ጦር መኮንኖች ጋር ግንኙነት ሲያደርጉ ነበር። ሁለቱም ሰዎች በማዕድን ዘርፍ ላይ የተሰማሩ እንደሆኑ እና ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በመደበኛነት የሚመላለሱ መሆናቸው  ጥርጣሬን አጭሯል። ከፈረንሳይ አምባሳደር መኖሪያ ቤት አጠገብ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ላይ በተደረገ ፍተሻ በርካታ የጦር መሳሪያዎች፣ ወታደራዊ ዩኒፎርሞች እና በርካታ ገንዘቦች ተይዟል። ሁለቱ ሰዎች እ.አ.አ ሰኔ 10 ቀን በፖሊስ ተይዘው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በምርመራ ተቋሙ መሥሪያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ። ተጠርጣሪዎቹ  የፈረንሳይ እና የአልጄሪያ ፓስፖርት ሲኖራቸው፤ የዱባይ የመኖሪያ ፈቃድ እንዳላቸው ተገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0