የሰኔ 6 ረፋድ ዋና ዋና የአለም ዜናዎች፡-

ሰብስክራይብ
የሰኔ 6 ረፋድ ዋና ዋና የአለም ዜናዎች፡- 🟠 የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር ሶስት የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች ትላንት በአንድ ሌሊት በሩሲያዋ ያሮስቪል እና  ቭላድሚር ክልል ላይ መትተው መጣሉን ገለጸ። 🟠 ትላንት ምሽት በአርሜኒያ የፓርላማ ህንፃ አቅራቢያ በተነሳ ግጭት፤ ፖሊሶችን ጨምሮ ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ 101 የሚደርሱ ሰዎች ፤ መቁሰላቸውን የሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልጿል። 🟠 የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ በ ቡድን ሰባት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለዩክሬን የ310 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ እንደሚሰጡ ፅህፈት ቤታቸው አስታውቋል። 🟠 አሜሪካዊው ኢሎን መስክ የዩክሬን መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን አሜሪካ  በ"ጥቁር መዝገብ" በአሸባሪነት ዝርዝር እንድትመዘግባቸው እና ማዕቀብም እንዲጣልባቸው ጥሪ አቅርቧል። 🟠  በሁለተኛው የሩሲያ ስትራቴጂክ ያልሆኑ የኒውክሌር ሃይሎች ልምምድ ወቅት የኤሌክትሮኒካዊ ሚሳኤል ማስወንጨፉን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0