ሩሲያ እና 20 የሚደርሱ ሀገራት በፈጠራ ስራዎች ላይ የሚሠራ ቡድን እንዲሁም ሰው ሰራሽ አስተውህሎን በትምህርት መስክ በማካተት በትብብር ለመመስረት ተሰማሙ

ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና 20 የሚደርሱ ሀገራት በፈጠራ ስራዎች ላይ የሚሠራ ቡድን እንዲሁም ሰው ሰራሽ አስተውህሎን በትምህርት መስክ በማካተት በትብብር ለመመስረት ተሰማሙ የሩሲያ የትምህርት ሚኒስትር ሰርጌ ክራቭትሶቭ እና ከ 20 ሀገራት የተወጣጡ ልዑካን ቡድን መሪዎች፤ ቬኔዙዌላ፣ ኒጀር፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ ኩባ፣ ላኦስ፣ ጋምቢያ፣ ኡጋንዳ እና ዚምባብዌን ጨምሮ በፈጠራ ሙያዎች ላይ የሚሠራ ቡድን መመስረታቸውን  አስመልክቶ ተፈራርመዋል። የሰው ሠራሽ አስተውህሎን፤ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ እንዲሁም የምህንድስና ትምህርት ቤቶችን ማቋቋም ያካትታል። የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ የተካሄደው በሩሲያ ካዛን ከተማ እ.አ.አ ከሰኔ 10-11 "የወደፊቱን መቅረጽ" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ሚኒስትሮች ጉባዔ ወቅት ነው። በመግለጫው መሰረት የተቋቋመው ቡድኑ  በፈጠራ ሙያ፣ በሰው ሰራሽ አስተውህሎ እና በምህንድስና ትምህርት ዘርፍ ሀገራዊ ልምድ ልውውጥ እንዲኖር የሚያስችል ነው። ይህ ዓይነት ልምድ፤ ሀገራት ጥራት ያለው፣ ተደራሽ እና የተሻሻሉ የትምህርት ውጤቶች እንዲመዘገቡ እድል ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0