ቱርክ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት ሩሲያ በደስታ እንደምትቀበለው ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናገሩ።
"ቱርክ ብሪክስ ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት በደስታ እንቀበላለን፤ይህንን ፍላጎት በሁሉም ረገድ እንደግፋለን፤ እናም የጋራ ችግሮችን ለመፍታት ከህብረቱ አባል ሀገራት ጋር በጋራ እንሰራለን" ሲሉ ከቱርኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን ጋር በነበራቸው ውይይት ገልፀዋል።
በተጨማሪም ሩሲያ ከቱርክ ጋር ባላት ግንኙነት ደስተኛ ነች ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
"ከቱርክ ጋር ባለን ግንኙነት ደስተኞች ነን። ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው በቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን አመራር እና ቀጥተኛ ድጋፍ ነው" ብለዋል ፑቲን።
ቭላድሚር ፑቲን በሚቀጥለው ወር ከቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር በአስታና የመገናኘት እቅድ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
" ለፕሬዚዳንት ኤርዶጋን መልካም ምኞቴን እንዲያደርሱልኝ እጠይቃለሁ ። እስከማውቀው ድረስን በሐምሌ ወር (ከሐምሌ 3-4 ) በአስታና በሚደረገው ስብሰባ ላይ እንገናኛለን የሚል ተስፋ አለኝ። በዚህ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ተገናኝተን ስለ ወቅታዊ ጉዳዮች የመወያየት እድል ይኖረናል ብዬ አምናለሁ። " ሲሉ ፑቲን ተናግረዋል።
ሃካን ፊዳን ከፑቲን ጋር ከመገናኘቱ በፊት የብሪክስ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባን በሩሲያዋ ኒዝሂ ኖቭጎሮድ ከተማ ታድመዋል።
ከስብሰባው ጎን ለጎን በተለይ ከኢትዮጵያ አቻቸው አምባሳደር ታዬ አጽቅስላሴ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ቱርክ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት ሩሲያ በደስታ እንደምትቀበለው ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናገሩ።
ቱርክ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት ሩሲያ በደስታ እንደምትቀበለው ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናገሩ።
Sputnik አፍሪካ
ቱርክ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት ሩሲያ በደስታ እንደምትቀበለው ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናገሩ። "ቱርክ ብሪክስ ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት በደስታ እንቀበላለን፤ይህንን ፍላጎት በሁሉም ረገድ እንደግፋለን፤ እናም የጋራ ችግሮችን ለመፍታት... 12.06.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-06-12T15:09+0300
2024-06-12T15:09+0300
2024-06-12T15:40+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ቱርክ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት ሩሲያ በደስታ እንደምትቀበለው ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናገሩ።
15:09 12.06.2024 (የተሻሻለ: 15:40 12.06.2024)
ሰብስክራይብ