ከ150 በላይ የሚሆኑ ከ40 ሀገራት የተውጣጡ ተሳታፊዎች በሩሲያ በተዘገጀው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ እየተሳተፉ ይገኛሉ

ሰብስክራይብ
ከ150 በላይ የሚሆኑ ከ40 ሀገራት የተውጣጡ ተሳታፊዎች በሩሲያ በተዘገጀው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ እየተሳተፉ ይገኛሉ በሁለተኛው ቀን የትምህርት ሚኒስትሮች ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የትምህርት ሚኒስትሮች ጉባኤ  "የወደፊቱን ሁኔታ መቅረጽ" በሚል መርህ ለሁለተኛ ጊዜ በተከታታይ አመት የአለም አቀፍ የትምህርት ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት ጉባኤ ፤የሩሲያ የትምህርት ሚኒስትር ሰርጌይ ክራቭትሶቭ ያለፈውን ዓመት ጉባኤ ውጤቶቹ ለተሰብሳቢዎቹ ገለጻ አድርገዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ በዚህ ዓመት በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ 40 አገሮች የተውጣጡ ከ150 በላይ ልዑካን ተሳታፊ ሆነዋል። "በሩሲያ የትምህርት ስርዓት ላይ ፍላጎት ያሳዩ ወዳጅ ሀገራት መኖራቸውን አይተናል። በጉባኤው ላይ ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት የተወጣጡ ከ 150 በላይ ልዑካን ይሳተፋሉ ። ከአንድ ዓመት በፊት ካደረግነው የመጀመሪያ ጉባኤ ውጤቶች አንዱ የኢንተርኔት  መረብ  ውስጥ ጭምር ሥራዎችን መሥራት መጀመራቸውን ሚኒስትሩ በአፅንዖት ተናግረዋል። እንደ ክራቭትሶቭ ገለጻ፣ ዓለም አቀፍ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ሩሲያ በ2023 የትምህርት ጥራትን በማስመዝገብ ከዓለም 10 አንደኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በትብብር ረገድ ሩሲያ "ይህንን ወይም ያንን ርዕዮተ ዓለም ላለመጫን መርህን ታከብራለች" ነገር ግን "እያንዳንዱን ሀገር ታከብራለች" ሲል አስምሮበታል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0