በምእራብ ሱዳን በትንሹ 6 ህፃናት መሞታቸውን ዩኒሴፍ አስታወቀ

ሰብስክራይብ
በምእራብ ሱዳን በትንሹ 6 ህፃናት መሞታቸውን ዩኒሴፍ አስታወቀ በሰሜን ዳርፉር ግዛት ኤል ፋሸር ካለፈው አርብ ጀምሮ ውጊያው ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ በትንሹ 6 ህጻናት መሞታቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን የሚገልጹ አሳዛኝ ዘገባዎች ደርሰውናል ሲሉ የዩኒሴፍ የመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር አዴሌ ኮደር ተናግረዋል። ከግንቦት መጀመሪያ ጀምሮ በምዕራብ ሱዳን የሚገኘው የሰሜን ዳርፉር ግዛት በተለይም ዋና ከተማዋ ኤል ፋሸር በ ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች (RSF) እና በሱዳን ጦር መካከል ካለፈው ሚያዚያ ወር ጀምሮ ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉ ተነግሯል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0