በግብፅ 660,000 የሚጠጉ ስደተኞች መመዝገባቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኮሚሽነር አስታወቁ።

ሰብስክራይብ
በግብፅ 660,000 የሚጠጉ ስደተኞች መመዝገባቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኮሚሽነር አስታወቁ። በሱዳን በተፈጠረው ችግር የስደተኞች ቁጥር ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር ክርስቲን ቤሻይ በካይሮ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል ። ይህም ከጠቅላላ የስደተኞች ቁጥር 378,000 ያህሉ የሱዳን ዜጎች መሆናቸውን ገልጸዋል። እ.ኤ.አ ከሚያዝያ 15፣ 2023፣ በሱዳን ጦር እና በ ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች መካከል ግጭት ተፈጠረ። በግጭቱ ተሳተፊ የሆኑ ወገኖች በ Uገር አቀፍ ደረጃ በተደጋጋሚ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ቢሞክርም፤ ለግጭቱን እልባት ማግኘት አልተቻለም። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0