የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ እንደሚገኙ ታወቀ

ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ እንደሚገኙ ታወቀ የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር፤ በሩስያዋ ኒዝሂ ኖቭጎሮድ ከተማ በሚካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ፤ የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል። ፓንዶር፤ በውይይቱ ወቅት ከብሪክስ ሀገራት አንዳንድ የስራ ባልደረቦች እና ሌሎች አጋር ሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ እንዳቀዱ፤ መግለጫው አመልክቷል። የስብሰባው ውጤት ሩስያ ካዛን ውስጥ "በጥቅምት ወር ለሚካሄደው 16ኛው የብሪክስ ጉባኤ እንደሚያገለግል" ተገልጿል። ሩስያ፤ ከ20-25 ሀገራትን እንደምትጠብቅ እና 15 ተጨማሪ የሩስያ "ወዳጅ" ሀገራት፤ ቀጠናዊ የውህደት ድርጅቶች መሪዎችን ጨምሮ፤ በስብሰባው ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸውን፤ የሩስያ የብሪክስ ተወካይ ፓቬል ክንያዜቭ ከዚህ በፊት ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0